Wednesday, October 31, 2012

የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ዋና ዋና 
  • የአብነት ትምህርት ቤቶችን ገዳማትንና የካህናት ማሠልጠኛዎችን በበጀት አጠናክሮ በበለጠ እንዲሠሩ ለማድረግ የ10 ሚሊየን ብር በጀት እንዳጸደቀ አመልክቷል፡፡
  • እርቀ ሰላሙ በመጪው ህዳር ወር የሚቀጥል ይሆናል 
  • ቅዱስ ሲኖዶስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለአራት አህጉረ ስብከት እንዲከፈል ወስኗል
  • የአቡነ ጰውሎስ ንብረት በሙሉ ተሰብስቦ ወደ ሙዝየም እንዲገባ ሲኖዶስ ወስኗል
  • ዱስ ሲኖዶስ ለዕርቀ ሰላሙ ውይይት የወከላቸው ሦስት ብጹአን አባቶች ኀዳር 25 ቀን ወደ አሜሪካ አምርተው ውይይቱ ከኀዳር 26-30 ቀን 2005 ዓ.ም በዳላስ ቴክሳስ እንደሚካሄድ ታውቋል:: 
  • የሥርዐተ ምንኵስና አፈጻጸም በየገዳማቱ ሕግ መሠረት ጠብቆ “ልማት እንዲጠናከርባቸው” ይደረጋል::
  •  የካህናት ማሠልጠኛዎች በየክልሉ ይቋቋማሉ፤ በየቋንቋዎቹ የመጽሔቶችና ጋዜጦች ኅትመት ይጀመራል::
  •  
  • †♥† ነገረ ቅዱሳን †♥†


    †በስመ ሥላሴ†
    “ስምከ ሕያው ዘኢይመውት”/”ሰው የተመኘውን ከሰራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው”  (አባ ጎርጎርዮስ ሊቀ ጳጳስ 1932-1982)
     ወበዛቲ ዕለት አዕረፈ አቡነ አላኒቆስ (ጥቅምት ፳፩) (በዚህ ቀን ትልቁ ጻድቅ አቡነ አላኒቆስ አረፈ)።  

    “ከቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር (የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።”) መዝ.፻፲፭/፻፲፮፡፲፭ (115/116፡15

    ሀገራቸው ሸዋ አንኮባር ሲሆን ወግዳ ወይም ምግዳ ይላቸዋል። አባታቸው አጼ ይኩኖ አምላክ እናታቸው ንግስት ኮከቢያ ይባላሉ። የንጉስ ልጅ ሲሆን መናኔ መንግስት ወብእሲት ናቸው። የተወለዱትም በ1238 ዓ.ም ነው። እንቁ ባህርይ የመል የቅዕል ስም አላቸው። ንጉሱ አባታቸው አግባና መንግስቴን ውረስ ሲላቸው እምቢ ብለው ወደ እመቤታችን ስዕል ሄደው ተደፍተው አለቀሱ። እመቤታችንም ክፍልህ ምናኔ ነው ስትላቸው የአባታቸው መንግስት እንደሚያል የእግዚአብሔር መንንግስት ብቻ ነው የማያልፈው ብለው ወደ ወሎ ሐይቅ ሄደው ተናደው ተወርውረው ከባህር ገቡ። በዚያን ጊዜ መላእክት መጥተው አወጡአቸውና አፅናነትው በዚህ ገዳም እንዲቀመጡ ከአበምኔቱ ጋር አገኛቸው። በዚህ ገዳም መንኩሰው ወደ አክሱም ገዳም ሄደው የታቦተ ሙሴ አጣኝ ሆኑ። ትልቁ ታሪካቸውም ጓደኛቸው ከእሳቸው ጋር አብረው የሚኖር መነኩሴ የሚያገለግላቸውም ነበርና በንሰሐ አባትነት የያዟት አንዲት ሴት ነበረች። በዚህ ጊዜ ከአሽከሯ አረገዘች፤ በኋላም በሏ መኮነኑ ከዘመቻ ሲመጣ ከምን አረገዝሽው ብሎ ቢጠይቃትና ቢገርፋት ሲጨንቃት ከንሰሐ አባቴ ነው ያረገዝኩት ብላ ንሰሐ አባቷን በሐሰት ወንጅላ ወስዳ ሰጠችው። ከዚህ በኋላ ያነን መነኩሴ እገድላለሁ ብሎ ወደ ገዳሙ ሄደ። አቡነ አላኒቆስም ይህንን ነገር ሰሙ።  ወደ እኔ ኑ ብለው ጠሩአቸው። ያም በሐሰት የተወነጀለው መነኩሴ ሄዶ ወደ አቡነ አላኒቆስ ተጠግቶ አለቀሰ። ሰገደ ጻድቁም እሷን አስጠርተው ሲጠይቋት ስታፍር አዎን አለች፤ በሐሰት በዚህም ጊዜ ከሱ ከሆነ ይወለድ ከሌላ ከሆነ ግን አይወለድ ብለው ገዘቷትረገሟት፤ በሆዷ ይዛ 22 ዓመት ጢም አውጥቶ ጥርስ አብቅሎ ተወለደ። ህፃኑ ሲወለድም “ወእመሰ እምዘመደ እስራኤል ክብርት እንተ ረስየተኒ ገብረ”  በሎ መሰከረባት። ከዚህ በኋላ ህፃኑንም  አባታችን አሳድገውት ስሙንም አባ ተወልደ መድህን ብለው አመንኩሰው በምናኔ እንዲኖር አድርገውታል። ግድልም አለው፤ ታቦትም አለው። በዕብላ ወረዳ አሉጌን ከተባለው ተራራ ላይ ገዳም አለው። እንግዲህ አባታችን ታሪካቸው እጅግ በጣም ብዙ ነው። ዛሬ ገዳማቸው የሚገኘው ትግራይ ማይበራዝዬ ነው። ይህን ሁሉ ተጋድሎ አድርገው አባታችን በክብር በዛሬዋ ቀን ዐርፈዋል።

    ዮሐንስ ሐጺር



    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን፡፡
    አባ ዮሐንስ ሐጺር ( ጥቅምት  አዕረፈ)

    “ከቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር (የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።”) መዝ.፻፲፭/፻፲፮፡፲፭ (115/116፡15

    እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን፡፡(እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል፤ እግዚአብሔር  ስደተኞችን ይጠብቃል፡፡)“ መዝ.፻፵፭፡፰ (145፡8)

        በዚህች ቀን አባ ዮሐንስ ሐጺር አረፈ።  ቁመቱ አጭር ስለሆነ ነው ዮሐንስ ሐጺር የተባለው። በ18 ዓመቱ በገዳመ አስቄጥስ መንኩሶ በተጋድሎኖረ ሲሆን ይህ አባትነጽሮተ ስሉስ ቅዱስ” የደረሰ አባት ነው።

        እዚህ ደረጃ የደረሱ አባቶች ቀና ቢሉ ሥላሴን ይመለከታሉ ዝቅ ቢሉ እንጦሮጦስን ያያሉ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን የገዳሙ አበምኔት ሊፈትነው ብሎ ደረቅ እንጨት ሰጠው ይህንን ተክለህ አለምልመህ ፍሬውን አምጣልኝ አለው።

        እርሱም እንጨቱን ተከለውና፤ 3 ዓመት ሙሉ ከሩቅ ቦታ ውሃ እየቀዳ አጠጣው።  3ኛው ዓመት ጸደቀ፤ ለመለመ፤ ትልቅ ዛፍም ሆነ፤ ፍሬም አፈራ፤ መነኮሳቱ ይህ የትእግስት ውጤት ነው ብለው ፍሬውን ቀምሰውለታል፡፡

        አንዲትአትናስያ” የምትባል ሴት ነበረች። መጀመሪያ ጻድቅ ነበረች በኋላ ላይ በዝሙት ወደቀች ዘማዊም ሆነች። የቀድሞ ቅድስናዋን የሚያውቁ መነኮሳት ሊመክሯት ቢመጡ ሳቀችባቸው። አሁን ማንን እንላክ ብለው አሰቡ ዮሐንስ ሐጺርን ላኩት። ተራ ሰው መስሎ ገባ፤ ለዝሙት የመጣ መስሏት ተቀበለችው። ተጫወት አለችው ዮሐንስ ሐጺር ማልቀስ ጀመረ ምን ያስለቅስሃል ትለዋለች።

    Tuesday, October 30, 2012

    ጸጋ ትኅትና

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን፡፡ 
    ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ ያደረሱን “ፍቅረ መድኅን” የተሰኙ ተርጓሚ(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን 113ኛ አበ አበው (ፓትርያርክ) እንደ ጻፉት) ሲሆኑ እኛም ጽሁፉ የያዘውን ቁመ ነገር ለእናነተም ልናካፍላችሁ ወደድን ተርጓሚውን አምላክ በእድሜ በፀጋ ይጠብቅልን፡፡ መልካም ንባብ፡፡                                                                                              ውርስ ትርጉም - በፍቅረ መድኅን
                                                                                የእንግሊዝኛው ርእስ- The Virtue of Humility
     እመቤታችን እና ንግሥታችን የምትኾን፤ የቅድስተ ቅዱሳን ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያምን በዓል ምክንያት አድርገው    የመንፈሳውያን ዓርማ፤ የአጋንንት መውጊያ ስለኾነችው ስለ ትኅትና ቅዱሰነታቸው አቡነ ሲኖዳ ካስተማሩት

    የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን በዓል ምክንያት አድርገን ከታደለቻቸው ጸጋዎቿ አንዱ ስለኾነው ጸጋዋ እንነጋገራለን፡፡ይኸውም ትኅትና ነው፡፡
    በመንፈሳዊ ሕይወት ትኅትና ቀዳሚው ጸጋ ነው፡፡ትኅትና በመንፈሳዊ ሕይወት ግንባር ቀደም በመኾን ጸጋን እና ተሰጥዖን ይጠብቃል፡፡በትኅትና ያልታጀበ ወይንም ከትኅትና ጋር ያልኾነ ጸጋ ኹሉ በግብዝነት የተነሣ በሰይጣን ሊነጠቅ፤ በኩራት በመመካት እና ራስን በማድነቅ የተነሣ ሊጠፋ ይችላል፡፡
    ወዳጄ: እግዚአብሔር ማንኛውንም ዓይነት ስጦታ ቢሰጥህ ከስጦታው ጋር ትኅትናን  ጨምሮ እንዲሰጥህ ካልኾነ ግን ካንተ እንዲወስድልህ ጸልይ፡፡ በተሰጠህ ስጦታ የተነሣ በመመካት እንዳትጠፋ፡፡

    Friday, October 26, 2012

    እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል

    "እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል፤ የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል፤ እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።" መኃ.5:2              
    በዲ/ን ዳንኤል ክብረት