Friday, September 28, 2012

ብዙኃን ማርያም



መስከረም ፳፩
ብዙኃን ማርያም  
መከበሩ ስለ ሁለት ነገር ነው። አንዱ ጉባኤ ኒቂያን ይመለከታል።
፩ የመጀመሪያው ከተፍጻሜተ ሰማዕት አንዱ ከቅዱስ ጴጥሮስ ተማሪዎች አንዱ አርዮስ “ትቤ ጥበበ ፈጠረኒ አብ ከመ እኩን መቅድመ ኩሉ ተግባሩ” ያለውን ንባብ ይዞ “ወልድ ፍጡር ነው” ብሎ ተነስቶ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ እለእስክንድሮስ አውግዞት በዚህ ምክንያት በጉባኤ እንዲነጋገሩ የሮም ንጉስ ደጉ ቆስጠንጢኖስ በኒቂያ ጉባኤ ይሁን ብሎ አዋጅ አስነግሮ የመስከረም 21 ዕለት በ2340 (43) ሊቃውንት በኒቂያ ተሰብስበዋል።
፪. “መስቀልን ይመለከታል።”
“በምድር ላይ ኃጢአትን አሰረ፤ በሲዖል ሞትን አሸነፈ፣ በመስቀል ሳለ መርገምን ሻረ፣ በመቃብር ውስጥ ፈርሶ በስብሶ መቅረትን አስቀረ። (ቅዱስ አትናቴዎስ)
የጌታ ግማደ መስቀል በብዙ እንግልትና መከራ በግብጻውያን ከተወሰደብን በኋላ የግብጻውያንንም ኑሮ በግዮን ውሃ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ይግዮንን ውሃ በመገደብ በኋላ ላይ ግብጻውያን አማላጅ ልከው መስቀሉን እንመልስላችኋለን ውሃውን ልቀቁልን በማለት በብዙ መከራ እንደመጣ የቤተ ክርስቱያናችን ታሪክ ይገልጻል።   በወቅቱም በሀገሪቱ ሰማይ ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ከመስጠት ተከልክሎ ምድርም የዘሩባትን ከማብቀል የተከሉባትን ከማጽደቅ ተከልክላ ረሃብ ሆኗልና፤ ምናልባት ጌታ ቢታረቀን ከመስቀሉ አንዱን ወገን ላኩልን ብለው ጽፈው እጅ መንሻ ጨምረው ላኩ። ይገባዋል ብለው መክረው ዘክረው የቀኝ ክንዱ ያረፈበትን፣ ስዕለ ተኮርዖውንና ቅዱስ ሉቃስ የሳላትን ስዕለ ማርያም ላኩላቸው።
 ደግማዊ ዳዊትም ሊቀበሉ ስናር ድረስ ወርደው በእልልታ በሆታ ተቀብለው ሲመለሱ እሳቸው ባዝራ ጥላቸው ከመንገድ ዐርፈዋል።

ዕረፍቱ ለቅዱስ ኤውስጣቴዎስ



በስመ ሥላሴ
መስከረም ፲፰
ወበዛቲ ዕለት አዕረፈ ጻድቅ (ቅዱስ) ኤውስጣቴዎስ) (1215-1313)
†”ከቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር  /“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” መዝ.፻፲፭/፻፲፮፡፲፭/ መዝ.115/116፡15
“ቅዱሳን በመለኮታዊ ማዕጠንት የተቀጣጠሉ ዕጣን ሲሆኑ የተቀጣጠሉበትም በፈጣሪያቸው ፍቅር ነው።” (ብጹህ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ)
አባታቸው ክርስቶስ ሞአ እናታቸውስነ ሕይወት ይባላሉ። በብስራተ መልአክ ወልደዋቸዋል። ዘካርያስ ለሚባል መምህር ሰጥተዋቸው ሲማሩ ሲያገለግሉ አደጉ። ኋላም መዓርገ ምንኩስናን  ተቀብለው በትኅርምት የሚኖሩ ሆነዋል። አንድ ቀን የነግህ ተግባራቸውን አድርሰው ከመካነ ግብራቸው ተቀምጠው ሳሉ ጌታ እንዲረዳቸው ሆኖ ተገልጾ ለኢትዮጵያና ለአርመንያ ሐዋርያ እንድትሆን መርጬሃለሁና ዙረህ አስተምር ”አንተን የሰማ እኔን ሰማ አንተን ያልሰማ እኔንም አልሰማም” አላቸው። እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።” ማቴ.፲፡፵ (10፡40) እንዲል። መዓርገ ቅስና ተቀብለው ማስተማር ጀመሩ።
አንድ ቀን ቅዱሳት መካናትን እጅ ለመንሳት ስድስቱን ቀን እየተጓዙ ሰንበትን እያረፉ ኢየሩሳሌም ደርሰው ሲመለሱ እግረ መንገዳቸውን ወደ አርመንያ ሲሄዱ ባሕረ ኢያርኮ ደረሱ። መርከበኛ አግኝተው እንዲያሳፍራቸው ጠይቀውት ትቷቸው ሄደ። የለበሱትን አጽፍ ከባሕሩ ላይ አንጥፈው ልጆቼ ጥበበ እግዚአብሔርን እመረምራለሁ ሳትሉ ተሳፈሩ አሉ። ተሳፍረው ሲሄዱ ተጠራጥሮ የነበረ አንድ ደቀ መዝሙር የመርፌ ቀዳዳ በምታህል ቀዳዳ ሾልኮ ሰጥሟል። እርሳቸው ግን ከነደቀመዛሙርቶቻቸው ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በግራ በቀኝ ሆነው እየቀዘፉ አሻግሯቸዋል። ኋላ ግን ያን ደቀመዝሙር ጸልየው አድነውታል። አንተ እምነት የጎደለህ፥ ስለምን ተጠራጠርህ? አለው። ወደ ታንኳይቱም በወጡ ጊዜ ነፋሱ ተወ። ማቴ.፲፬፡ ፴፩-፴፪ (14፡31-32)

ስለ መስቀል ክፍል ሁለት


በስመ ሥላሴ 
ሁሉን ቻይ ታላቅ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፣ በቀንና በሌሊት የአንተን መኖር አስታውስና፣ አንተን ሁል ጊዜ በፊቴ አደርግህ ዘንድ ልቤን ምራልኝ፤ በኪሩቤል ላይ የምትኖር የቀለያትንም (ጥልቅ ባሕርንም) ጥልቀት የምትመለከት ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ፤ አቤቱ ምስጢርን ግለጽልኝ፤ ቃልህንም እናገር ዘንድ፣ ያለመሰልቸት ስለ አንተ እንድመሰክር አንተ አንደበት ሁነኝ አሜን።
“በምድር ላይ ኃጢአትን አሰረ፤ በሲዖል ሞትን አሸነፈ፣ በመስቀል ሳለ መርገምን ሻረ፣ በመቃብር ውስጥ ፈርሶ በስብሶ መቅረትን አስቀረ። (ቅዱስ አትናቴዎስ)
“መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር” (መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው)” (ሊቃውንተ ቤ/ክ)
እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ከፈጠረበት ጥበቡ በሚበልጥ ዓለምን ሁሉ ያዳነበት ከጥበብ ሁሉ በላይ የሆነ ጥበብ ይህ ቅዱስ መስቀል ነው!”
    
በቀደም በክፍል ፩ (አንድ) ጽሑፌ መስቀል በመጽሐፍ ቅዱስ በሦስት ከፍዬ ማሳየቴ ይታወሳል፤ ይህም  ፩. መከራ መስቀለ ክርስቶስ
                 ፪. መከራ መስቀለ ክርስቲያንና
                 ፫. ዕፀ መስቀል
የመጀመሪያውን መስቀል ማለት መከራ መስቀለ ክርስቶስን መሆኑን  በቀደም በጻፍኩት ጽሑፌ በሰፊው የገለጽኩት ሲሆን፤ በክፍል ሁለቱ (፪)ቱ ደግሞ የቀሩትን ማለትም፡- መስቀል ማለት “መከራ መስቀለ ክርስቲያንና”፣ “ዕፀ መስቀል” በሚሉት ትርጉሞች ላይ ዳግም ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘን መለያየታችን ይታወሳል።
ክፍል ሁለት ደግሞ እነሆ እንደሚከተለው ቀርቧል።  መልካም ንባብ ይሁንላችሁ።
፪. “መከራ መስቀለ ክርስቲያን”፡- ማለት አንድ ክርስቲያን ወይም ሐዋርያ ስለ ክርስቶስ ስም፣ ስለ ወንጌል፣ ስለ ቤተክርስቲያን እድገት፣ ስለ ማህበረ ምዕመናን፣ የሚደርስበት መከራ፣ ስድብ፣ ሐሜት፣ መስቀል ይባላል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲናገር “መስቀሌን የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለኔ ሊሆን አይገባውም።” ማቴ.፲፡፴፰/10፡38/ በማለት የተናገረው ለዚህ ነው። በተጨማሪም “እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር እራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። አለ (ማቴ.፲፮፡፳፬/16፡24/፣ ማር.፰፡፴፬-፴፮/8፡34-36/ ጌታ መስቀሉን ተሸክሞ እንዳለ ቅዱሳን ሰዎች የሚቀበሉት የክርስቶስ ሳይሆን የራሳቸውን ነው። በመሆኑም ቅዱስ ጴጥሮስ ቁልቁል መሰቀሉ፣ ቅዱስ ጳውሎስ በሰይፍ መመታት፣ ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ኢሳያስ በመጋዝ መተርተራቸው የቅዱሳን ሁሉ ልዩ ልዩ ጸዋተወ መከራ መስቀል ይባላል።

Thursday, September 27, 2012

በዋልድባ አምላከ ቅዱሳን ተዓምራቱን እያሳየ ነው

የገዳማውያኑ የጸሎታቸው በረከት ይደርብን
  • ቅዱስ ሩፋኤል በእለተ ቀኑ በዋልድባ ዛሬማ ወንዝ ላይ የተሰራውን ድልድይ በመብረቅ ተመቶ ጠራርጎ ወስዶታል
  • በአቲካ ወንዝ ላይ የተሰራው የሸንኮራ ማልማያ ግድብ እንዲሁ በዚሁ ቀን ፈራርሷል
  • የገዳማውያኑ እንግልት እንደቀጠለ ነው
  • ቤተክህነት በዋልድባ ገዳም ለሚፈርሱት ቤተክርስቲያኖች ካሳ ጠይቋል ይባላል (የተረጋገጠ መልስ ማግኘት አልቻልንም)
(PDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ )
ባለፉት ጥቂት ሳምትታት ውስጥ በዋልድባ ገዳም አካባቢ በሚሰራው የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ የቻይናው ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ሥራውን ቀን ከሌሊት በመስራት ላይ እንደነበረ ከአካባቢው በደረሱን መረጃዎች ለመገንዘብ ችለናል። እንደሚታወቀው ከጥቂት ወራት በፊት በዋልድባ ገዳም አካባቢ ሊሰራ የታሰበውን ፕሮጀክት ሙሉ ለሙሉ ሃላፊነቱን ወስዶ ሥራዎቹን ጀምሮ የነበረው የሱር ኮንስትራክሽን በተለያየ ጊዜ በአካባቢው በደረሰው ተአምራት ለምሳሌ ለመጥቀስ ያህል የዲይን ኢንጂነሩ በአጋጣሚ በመሞቱ፣ ጥቂት ሰራተኞች በአውሬ በመበላታቸው፣ የግድቡ ሥራ በጣም አዳጋች በሆነ መልኩ መስራት ባለመቻላቸው (ለግድብ ሥራ ጉድጓድ ቆፍረው በነጋታው ሲመለሱ ውሃ ሞልቶት ወይንም አፈር ተንዶ በመሞላቱ) ተደጋጋሚ ክስተቶች በመፈጸማቸው የሱር ኮንስትራክሽን ኮንትራቱን አፍርሶ መውጣቱ ይታወሳል። ኮንትራት አፍርሶ መውጣት (breach of contract) በብዙ ሚሊዮን ብር ቅጣት የሚያስቀጣ ቢሆንም ሱር ኮንስትራክሽን ባለቤቶቹም ኢትዮጵያውያን በመሆናቸው የእግዚአብሔርን ተአምራት በዓይናቸው በማየታቸው ቅጣቱን ተቀጥተው ትተው ወጥተው ነበር።

Wednesday, September 26, 2012

“መስቀል መልእልተ ኩሉ ነገር ያድኅነነ እም ጸር - ከሁሉ በላይ የሆነ መስቀል ከጠላታችን ያድነናል!“ ቅዱስ ያሬድ



 “ሩቤል ላይ የምትኖር የቀለያትንም (ጥልቅ ባሕርንም) ጥልቀት የምትመለከት ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ አቤቱ ምስጢርን ግለጽልን፤ ቃልህንም እንናገር፣ እናስተላልፍም ዘንድ ሁኔታዎችን ሁሉ አመቻችልን።
+++ ዝንቱ መስቀል ረድኤት ወኃይል +++ ለእለ ነአምን መራሔ ሕይወትነ +++
+++
ይህ መስቀል ለምናምን ለኛ ሕይወትን የሚመራ ረድኤትና ኃይላችን ነው +++
ቅዱስ መስቀል
መስቀል በመጽሐፍ ቅዱስ በሦስት ይከፈላል። . መከራ መስቀለ ክርስቶስ
                                      . መከራ መስቀለ ክርስቲያን
                                      . ዕፀ መስቀል
. መከራ መስቀለ ክርስቶስ ማለት፡-  
ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ከጎልጎታ እስከ ቀራንዮ አደባባይ፣ ከዚያም እስከ ርደተ መቃብር የደረሰበት ጽኑ መከራ መስቀል ይባላል። የመስቀል ትርጉም ቅሉ መከራ ማለት ነው።
 ጌታችን በበረት መወለዱ፣ በጨርቅ መጠቅለሉ፣ በብርድ መንከራተቱ መስቀል ነው።
ወደ ግብጽ ተሰዶ እኛን ከስደት ነፍስ መመለሱ፣ሰይጣንን ከሰዎች ልቦና ማሳደዱ መስቀል ነው።
በአጠቃላይ ስለኛ የተቀበለው መከራ ሁሉ መከራ መስቀል ይባላል። ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና። ፩ቆሮ.፩፡፲፰ (1ቆሮ.118) በማለት የገለጸው። በተጨማሪም እንዲህ አለ ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ። ገላ.፮፡፲፬ (614) 

"ህንጸተ ቤተ ክርስቲያን"



"ሐነጽዋ ለቤተ ክርስቲያን" (ቤተ ክርስቲያንን ሰሯት)
“ቤተ መቅደስህ ቅዱስ ነው በጽድቅም ድንቅ ነው።” መዝ.፷፬/፷፭፡፭
 “በኢሩቤል ላይ የምትኖር የቀለያትንም (ጥልቅ ባሕርንም) ጥልቀት የምትመለከት ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ አቤቱ ምስጢርን ግለጽልን፤ ቃልህንም እንናገር፣ እናስተላልፍም ዘንድ ሁኔታዎችን ሁሉ አመቻችልን።”

ይህ ዕለት መስከረም ፲፮ (16) ቀን ብቻ ህንጸተ ቤተ ክርስቲያን ይባላል:: በዚህ ቀንም እንደ ሌሎቹ ቀናት ሁሉ አምልኮተ እግዚአብሔር በመዝሙር በቅዳሴ ይደገማል።
የመዝሙሩ ርዕስ፡- "ሐነጽዋ ለቤተ ክርስቲያን" (ቤተ ክርስቲያንን ሰሯት)
በቅዳሴ ጊዜያትም ፩. በዲያቆኑ (ገባሬ ሰናዩ) 1ቆሮ.3፡1-18 ያለውን ፪. ዲያቆን (ንፍቁ ዲ.) ራዕ.21፡10 ፫ ረዳቱ ቄስ (ንፍቁ ካ.) ሐዋ.7፡44-51 ያነባሉ።
ምስባክ፡- በገባሬ ሰናዩ (ዋናው) ዲያቆን የሚሰበከው ምስባክ
ደብረ ጽዮን ዘአፍቀረ
ሐነጸ መቅደሶ በአርያም
ወሰረራ ውስተ ምድር ዘለዓለም
አማርኛ፡- የወደደውን የጽዮንን ተራራ።
        መቅደሱን እንደ አርያም ሠራ፥
        ለዘላለምም በምድር ውስጥ መሠረታት። መዝ.77(78)፡69
ምስጢር (ትርጉም) ይህ ምስባክ ደ/ጽዮን (ቤተ መቅደስን፣ እመባታችንን፣ ምዕመንን) የወደደ እርሱ እንደወደደ መመስገኛ የምትሆን ቤተ መቅደስን በልዕልና ሰራት፤ እመቤታችንን ለማደሪያው ፈጠራት፤ ምዕመንንም በሞቱ በደሙ ቀድሶ ማደሪያው አደረጋት፤ በዚህ ዓለም (እመቤታችን በክብር ምዕመናን በሕይወት በክብር አጽንቶ ሰራት የሚያሰኝ ትርጉም የያዘ ነው።
በዚህ ዕለት የሚነበበው የወንጌል ክፍል (በዋናው ቄስ) ዮሐ.10፡22 እስከ ፍጻሜው ድረስ።

“አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረን፤ እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፋችንን ደምስስ። ከበደላችንም ፈጽሞ እጠበን፥ ከኃጢአታችንንም አንጻን፤ እኛ መተላለፋችንን አናውቃለንና፥ ኃጢአታችንም ሁልጊዜ በፊታችን ነውና። አንተን ብቻ በደልን፥ በፊትህም ክፋትን አደረግን፥ በነገርህም ትጸድቅ ዘንድ በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ።” መዝ.50/51፡1-4'


ፀሎተ ምህላ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን።
“አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረን፤ እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፋችንን ደምስስ። ከበደላችንም ፈጽሞ እጠበን፥ ከኃጢአታችንንም አንጻን፤ እኛ መተላለፋችንን አናውቃለንና፥ ኃጢአታችንም ሁልጊዜ በፊታችን ነውና። አንተን ብቻ በደልን፥ በፊትህም ክፋትን አደረግን፥ በነገርህም ትጸድቅ ዘንድ በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ።” መዝ.50/51፡1-4

♥♥♥የይቅርታ አምልክ አቤቱ ማረን የቸርነት አምላክ አቤቱ ይቅር በለን፤ ልጅህን ልከህ ያዳንከን አቤቱ ተመልከተን ጨለማ ሕይወታችንን ወደ ብርሃን የለወጥክ  አቤቱ ታደገን።
♥♥♥በዚህ ክፉ ዘመን የገጠመንን መከራና ችግር ታርቅልን ዘንድ በአማኑኤል ስምህ በድንግል እናትህ እንለምንሃለን።
♥♥♥† በጨለማ ለነበሩት አህዛብ እንደ ነጋሪት ጮኸውመወለድህንና መምጣትህን ስላስተማሩ ነብያትህ ብለህ ከመዓት ሰውረን።
♥♥♥† የአህዛብን ምድር በመስቅልህ እርፍ አርሰው የቃልህን መዝገብ በዓለም ዳርቻ ሁሉ ስለ ዘሩ ስለ ቅዱሳን ሐዋርያት ብለህ ከክፉ መከራ አድነን።
♥♥♥† ድል ስለነሱ፣ አምነው ንጹህ ስለሆኑ ስለ ሰማዕታት ተኩላዎች ስለበሏቸው ስለመንጋህ ብለህ ይቅር በለን።

Tuesday, September 25, 2012

" ካልጠፋ ገላ ዓይን ጥንቆላ "

(ደቂቀ ናቡቴ መስከረም 15/2005) “የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።”ያዕ.5:16 በዋልደባ ገዳም መንግስት በጀመረው የስኳር ፋብሪካ ብዙ በጣም ብዙ በደሎች በመነኮሳቱ ደርሷል እየደረሰም ነው፡፡ እስከአሁንም ችግሩ እልባት ሳያገኝ በመነኮሳቱ ላይ ደብደባ እንግልት እና ከገዳሙ እንዲሰደዱ እየተደረገ ነው ፡፡ 
መነኮሳቱ ግን መፍትሄው እግዚአብሔር እንደሆነ ሁሉ እንባቸው ወደ አምላክ እየረጩ አምላክን ከመማፀን አልቦዘኑም፡፡ እንባን የሚያብስ አምላክ ግን ሁሉን ነገር በጊዜው ያደርጋል እያደረገም ነው የሚማር እና ከጥፋቱ የሚመለስ የለም እንጂ፡፡ ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ ያደረሱን “ፍቅር ይሄይስ ” የተሰኙ ፀሐፊ ሲሆኑ እኛም ጽሁፉ የያዘውን ቁመ ነገር ለእናነተም ልናካፍላችሁ ወደድን ፀሀፊውን አምላክ በእድሜ በፀጋ ይጠብቅልን፡፡ መልካም ንባብ፡፡ አምላካችን ሃገራችንን ይጠብቅልን፡፡  ቸር ወሬ ያሰማን፤ አሜን።                     
  " ካልጠፋ ገላ ዓይን ጥንቆላ "
  የሰው ልጅ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ እርስ በርሱ፣ በሀሳብና በድርጊቱ መካከል አለመግባባት ይፈጠራል፡፡ለዚህም የአዳምን ልጆች የአቤልንና የቃዬልን ህይወት ማንሳት የሰው ልጅ በተፈጠረ ማግስት አለመግባባትና የጥቅም እንደራሴነት አንደተጀመረ በቂ ማስረጃ ነው፡፡ በዘመናችን ከጉንጭ አልፋ ክርክርና ንትርክ አስከ ከፋ ግጭትና ሞት የሚያበቁ አለመግባባቶች የሚከሰቱት አንድም በስልጣን ወይም በጥቅም ይገባኛል የተነሳ ነው፡፡በነዚህ የግጭት ሰበቦች የተነሳ አለማችን ብዙ ሚለዮን ሰወችንና ብዙ ሀብትን አላግባብ አጣለች፡፡ ምናልባት የሰው ልጅ የአስተሳስብ አድማሱ እየጨመረ በመጣ ቁጥር ግን ልዩነቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ የመፍታት ሂደቱ እየጨመረ መምጣቱ ለመጭዋ ዓለም አበረታች ተስፋ ነው፡፡ የሰው ልጅ ከሶስት ነገሮች ጋር ሊጣላ ይችላል፡፡

Monday, September 24, 2012

ቅዱስ ያሬድ ዜማውና 1500ኛ አመት መታሰቢያ ክፍል ሶስት



ከባለፉት ሁለት ክፍሎች የቀጠለ
(ደቂቀ ናቡቴ መስከረም 14/2005)ቅዱስ ያሬድ ቀደምት የዜማ ምልክት ደራሲ መሆኑንም ጭምር ቤተ ክርስቲያን ለአለም የምታሳውቅበት ጊዜ ቢኖር ይህ 1500ኛ መታሰቢያ አመት ይመስለኛል ለዚህ የተቀደሰ ተግባር ደግሞ እያንዳንዳችን ከዛሬ ጀምረን በየአጥቢያችን ታላላቅ በአላትን ተንተርሰን የሚዘከርበትን ሁኔታዎችን መፍጠር ይገባል ከመስቀል በዓል አከባበር ቢጀምር ባዮች ነን፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት ዑደት ስፍር ቀምር የራሷን  ዜማ ያደላደለች አፍሪካዊት እመቤት ናት ብንል ጽልመት ሊጋርደው የማይችለው ገሀድ ነው፡፡ 
የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶች 
የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርስቶች በአምስት ይከፈላሉ እነዚህም ድርሰቶች አምስት ፅዋትወ ዜማ በመባል ይጠራሉ ፡፡ እነርሱም ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ዝማሬ፣ መጽስዕትና ምዕራፍ ይባላሉ፡፡ ነገር ግን አንዳንድ የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍት ላይ የቅዱስ ያሬድ ድርስቶችን በዜማ ይተበh ደረጃ ልዩነት እና አንድነት ያላቸውን በመከፋፈል አራት ይላሉ አነርሱም ድጓ ቅዳሴ ዝማሬ እና መዋስዕት ይላሉ   ይህን የሚሉት ድጓ ጾመ ድጓ እና ምዕራፍ አንድ አይነት የዜማ ይትበሀል ስላላቸውንደ አንድ ስለሚቆጥሯቸው በድጓ ውስጥ ስለሚያጠቃልሏቸው በመሆኑ አምስት ከሚሉት ጋር የሚጋጭ አይሆንም፡፡
·         ድጓ- ከጽሕፈቱና ከምልክቱ ብዛትና ክሳት የተነሳ ረቂቅ እስተግብዕ /ስብስብ/ ይባላል፡፡  ምክንያቱም የዓመቱን በዓላትና የሳምንቱ መዝሙራት ተሰብስበው ስለሚገኙ ነው፡፡ ድጓ ስብስብ ሙሾ፣ ቁዘማ መዝሙር፣ ሐዲስ፣ ፍፁም ማለት ነው ድጓ የቤተ ክርስቲያ ዜማ መድብል ሲሆን በውስጡ አራት ክፍሎች አሉ እነርሱም፡-
1.    ድጓ ዮሐንስ - ስለ መጥምቁ ዮሐንስ የሚናገር ሲሆን፣ የዮሐንስን መንገድ ጠራጊነት የሐዲስ ኪዳንን መሸጋገርያነት አንስቶ የዘመረበት ነው የሚዘመርበትም ወቅት ከመስከረም 1  እሰከ ኅዳር 30  
2.    ድጓ አስተምሕሮ - ጌታችን ያሰተማረውን ትምህርት ያደረገውን ተዐምራት     የሚያነሳ ነው ማቴ.52  ማር1 39 የሚዘመርበት ወቅትም ከታህሳስ 1 እስከ መጋቢት 30፡፡
3.ድጓ ጾም - የድጓው ሦስተኛ ክፍል በዓቢይ ጾም የሚባል ነዉ፡፡
4.    ድጓ ፋሲካ - የጌታችንን ለዓለም ቤዛ ወይንም ፋሲካ ሽግግር ራሱን መስጠቱን ያነሳል የዕርገትን የጰራቅሊጦስንና የክረምትን ነገር ያነሳል የሚዘመርበት ወቀትም ከሚያዝያ/ከትንሳኤ/ እሰከ ጳጉሜን መጨረሻ፡፡