Thursday, August 16, 2012

አወዛጋቢዋ ድንግል ማርያም ነኝ ባይዋ ሴት በድጋሚ ወደ ዜና ብቅ አለች

  • በአዲስ አበባ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በግድያ ወንጀል እና በተለያዩ ክሶች አቃቤ ሕግ ከሷታል፡፡
  • በሌላ በኩል ከአዲስ አበባ ውጪ በፊቼ ክስ ተመስርቶባታል፡:
  • ተከታዮቿ በአዳዲስ ምልምሎችም ከበፊቱ በዝተዋል፡፡
  • ተከታዮቿ ከደብረ ሊባኖስ  መስቀል ቤተ  በመግባት እና ደብሩ ቅዳሴ ላይ እያለ ቅዱሳኑን እና መስቀሉን በመሳደባቸው ግጭት  እና ብጥብጥ ፈጥረዋ፡፡ 
ከሰማናቸው በጣም አስገራሚ እና አሳዛኙ ከስተቶች መካከል የዚህች ድንግል ማርያም ነኝ ባይ  ሴት ጉዳይ ከሁሉም አስገራሚ እና አሳዛኝ እንዲሁ በደፈናው ተከታይ ማፍራት እንደሚቻልና የዋሐንን በቀላሉ በመያዝ እንደሚጠቀሙባቸው ያሳየል፡፡ ለካ በቀላሉ የሚታለል ሰው በዝቷልና ያሰኛል፡፡
ከዚህ በፊት በዚህችው ሴት ጉዳይ ካስነበብናችሁ ዋና ጉዳይ መካከል፡-
  •   እናቷ ከሞተች በኋላ ከእግዚአብሔር መልክት ልትነግራት እንደተነሳች ከዚህ ግዚ ጀምሮ ተከታዮች ይዞ ወደ ተለያዩ ገዳማት በመሄድ የማወዛገብ ስራዎች እንደሰራች
  •      በፆም ወቅት ሥጋ እንዲበሉ ማስገደዱን በሌሎች ጊዜዬም አብዝተው እንዲፆሙ ማስገደድ
  •   ተከታዮቿ ሰማያዊያን ነን የሚሉ እንደሆነ
  •      3ቱ ልጆቼንም የወለድኩት በመንፈስ ቅዱስ ነው ጠባቂዬ ተርፌሳ ዮሴፍ ማርያምን እንደሚጠብቃት የእኔ ጠባቂ ነው፡፡
  •      እየሱስ ክርስቶስ ከእኔ ይወለዳል…….
የሚሉ እና ብዙ የተለያዩ አስገራሚ ጉዳዮችን ሲባሉ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይሁንና አሁንም የማወዛገብ ስራዎቿን በመቀበል ብዙ የማደናገ እና የማወዛገብ ስራዎችን እየሰራች ትገናለች፡፡
በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከ36 በላይ የሚሆኑ የቅርብ ተከታዮቿ ጋር በመሆን በመስቀል ቤት በመግባት መስቀሉን  ጣዖት ነው በማለት ከፍተኛ ብጥብጥ በመፍጠሯ 36ቱም በፊቼ ከተማ እስር ቤት እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ ከፍተኛ ብጥብጥ በመፈጠራቸውም በላይ የማንነታቸን መለያ በሆነው መስቀለ ልይ ለፈፀሙት ተግባር  36ቱም በፍቼ ክስ መሰርተውባቸው ለትላንት ለነሐሴ 10 ተቀጥረው ነበር ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም የጣራውን ኮርኒሱን ሰንጥቄ አርጋለሁ የሚሉ ቃላቶችን  መሰንዘሯ ታውቋል፡፡
በ2004 ዓ.ም  ከ5 ጊዜ በላይ በከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረበች ሲሆን ተከታዮቿም ከበፊቱ የተለያዩ አዳዲስ ሰዎችም እንደተቀላቀሏት እና አብረዎት ያሉትንም ምስኪን ወንዶችንም በቅዱሳን ስም በመሰየም ተግባራቸውም የቅዱሳን ነው ማለቷ ተዘግቧል፡፡
እንዲሁም ክስ ከተመሰረተባት ጉዳይ ጥቂ
  •  ስጋ ወደሙ ነው በማለት ተከተዮቿን ደም እንደምታጠጣቸው በዓይናቸው የተመለከቱ እንደመሰከሩ
  • አንድ እናትም ልጄን ሳር እንዲበላ በማስገደድ እና በማጎሳቆል እንዲያርፍ አድርጋለች በማለት መስክረውባታል ክርክርም ላይ ናቸው
ሌሎች አያሌ ክስ  ያለበት ሲሆን በዚሁ ወርም ነሐሴ 18/19/ አዲስ አበባ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀጠሮ ላይ መሆኗን ተረድተናል፡፡

ለምዕመናን የምናስተላልፍው መልእክት ቢኖር ምዕመናንን የማደናገርና የማሳሳት ስራ ዛሬ የተጀመረ ስራ ባይሆንም የተለያዩ ስለቶችን በመያዝ በአንዲቷ ሃይማኖታችን ስም  እየተነሱ ብዙ የዋህ ክርስቲያኖችን ሲያታልሉ ኖረዋል የኖራሉም ነገር ግን ለቤተ ክርስቲያናችን የሚያመጣው ገፅታ ከፍተኛ ችግር በመሆኑ   አጥብቀን ልንዋጋቸው የሚገባ ጉዳይ ነው በቅርቡም እንደምናስታውሰው እና እናንተም እንደገለፃችኁልን አንድ ከጎንደር የመጣች ሴትም በዚሁ አመቤቴ ታናግረኛለች በማለ ብዙ ታላለቅ ሰዎችም የተከረየችበት ቤት ድረስ እንደሚሄዱ እና ሴትየዋ እራሷን አለማዊ መናኝ ነኝ በማለት እና መንፈስ ቅዱስ እንደሚታያት እና እመቤታችን እንደምታናግራት ነው የምትናገረው ሁለት ልጆች ሲኖራት የመጀመሪያዋ ከሌላ ሰው የተወለደች ሲሆን ሁለተኛውም ከሌላ ወንድ የተወለደ ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረች ወደ 20 አመት ይሆናታል ካህን የሚያደርገውን ሁሉ ታደርጋለች ለምሳሌ ቄደር ማስጠመቅ፣ ንስሃ ለሷ መናዘዝ፣ ቅባቅዱስ መቀባት የመሳሰሉትን ነገሮች ታደርጋለች ለምን ይሄ እኮ የካህን ስራ ነው ስትባልእመቤቴ በልዩ ትዕዛዝ ለኔ ሰጥታኝ ነው ካህናቶች ሴቶችን በሚቀቡበት ጊዜ እየተሰናከሉ ስለሆነ ይህን ስልጣን ለሷ እንደተሰጣት ትናገራለች የንስሃ ልጆቼ ከምትላቸውም አስራት ትወስዳለች፡፡  ብዙ የዋሃን አስታለች እያሳተችም ነው እውነትን በመዘንጋት በየጉራንጉሩ በሚነሱ አጉል እምነቶች እና ዲያቢሎስ ስልቱን በመቀያየር ቁጥር የሚሸነፉ ቤት ይቁጠረው ይህ ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን ከሚሰሩት ሴራ ተለይቶ የሚታይ  አይደለም ሁሉም የአንዲት ቤተ ክርስቲያንን ጥፋት የሚፈልጉ ፡  የራሳቸው ጥቅም እና የሚከበርበትን መንገድ የሚሹ በመሆናቸው ምዕመናን አጥብቀን ልንታገላቸው እና ልንከላከላቸው ይገባል፡፡ ዲያብሎስ ዝናሩን እስኪጨርስ የእኛም ትጋት ሊቀጥል  ይገባል፡፡ 
አምላካችን አግዚአብሔር ያመንውን እንዲያጸናን ያላመኑትን እና በጥርጥር የሚጓዙትን ወደ አሚነ ስላሴ እንዲመልስልን ፈቃዱ ይሁንልን አሜን፡፡

19 comments:

  1. Amen!!! kendenezih ayinet menafkan Amlak yitebken

    ReplyDelete
  2. Egziabher Amlak eske elete motachen betsenach haymanotachen endinkoy yirdan. Abetu yikir yibelat.

    ReplyDelete
  3. Egziabher amlak bekenach haymanotachen endintsena yirdan. AMEN!

    ReplyDelete
    Replies
    1. OH my Good people do bad things in Relliagne it difficult time! people have to protect by all thing

      Delete
  4. Amen! Debr Libanos Erbsawe Yetnswe Eude Ken Nebre Berbshwe Wekit, Ke Andshi Yemibliet Tekuse Tetkuseo Nebre Sew Gien Almotem , Keswea Erbshagea Abrew Mengisten Yemikwmeu Tenstew Nebre Aleu, Eswane Ene Gerupchwean Yizew, Lilawen Betkuse Betnewal, Yhe Alfeo Eude Ken Eza Dershe New Yesmuet, Abea Pawlosem Yhen Argagleu Belew Amuse Ken Metew Nebre, Lemjmryea Gize Aywachew, Agtami Honeo Mesea Yetgabzubet Bet Gebten Temgbebn EGZIABHER Betkirstyanchnen Yitbkilen Amen!

    ReplyDelete
  5. ከጎንደር የመጣች ሴት ብላችሁ ያላችኋት ደግሞ ምንድነች? እኔ የማውቃት ከሆነች ብዙ ተንኮል ነበረባት እንዲሁም ባልና ሚስትንም አፋታለች መፀሀፍም አላት የራሷገድል

    ReplyDelete
  6. egizabher haymanotachnin yitebikiln!!!!!!!

    ReplyDelete
  7. ወይ ፈትና ድግሞ በዚህ መጡ ይህ የሴጣን ውጊያ ነው የሚሰማው ሁሉ ቲያትር የሚመስል ምነው የዚች ቤተክርስቲያን እና ሐገር ፈተና ብዛብን መንግስትና መሪያለብት ይህ ሁሉ ሲደረግ ምን ማለት ነው የሰሙ ሰዎች ምንይላሉ ዝም ብለው ራሳቸውም ይሄዳሉ ሌሎች ስሄዱም ዝም ይላሉ ሂወት ሲጠፋ ይነቃሉ የቤተክርስቲያን አባቶች የንሰሓ ሊጆቻቸውን ጸበል ከመርጨት ባለፈ ማስተማርና መከታተል አለባቸው ሁሉም የሚጠፉት በዚህ ጉዳይ የዚች ቤከስቲያን ልጆች ናቸው፡፡
    ወደ ፈትና እንዳንግባ ተግትን እንድንጸልይ ይገባል እግዚያብሄር ይርዳን አሜን!!!

    ReplyDelete
  8. ወይ ፈትና ድግሞ በዚህ መጡ ይህ የሴጣን ውጊያ ነው የሚሰማው ሁሉ ቲያትር የሚመስል ምነው የዚች ቤተክርስቲያን እና ሐገር ፈተና ብዛብን መንግስትና መሪያለብት ይህ ሁሉ ሲደረግ ምን ማለት ነው የሰሙ ሰዎች ምንይላሉ ዝም ብለው ራሳቸውም ይሄዳሉ ሌሎች ስሄዱም ዝም ይላሉ ሂወት ሲጠፋ ይነቃሉ የቤተክርስቲያን አባቶች የንሰሓ ሊጆቻቸውን ጸበል ከመርጨት ባለፈ ማስተማርና መከታተል አለባቸው ሁሉም የሚጠፉት በዚህ ጉዳይ የዚች ቤከስቲያን ልጆች ናቸው፡፡
    ወደ ፈትና እንዳንግባ ተግትን እንድንጸልይ ይገባል እግዚያብሄር ይርዳን አሜን!!!

    ReplyDelete
  9. lenegeru yegedil metsahfochachu bemulu ra-ey tayen bemilu bendezich aynet kebatariwoch yetesfu aydelumn? liyunetu yesua bezi zemen mehonu new. lehaymanot endemitikenu yechristian tapela letfo silekirstos adagnnet minim silemayakew hizbachu bitikenu endet tiru neber. yenate yehaymanot kinat kirstosin kesekelut keayhud kinat gar anid new.

    ReplyDelete
  10. gudegna belat bewinet behayimanotachn mtnker endalebin yasayenal

    ReplyDelete
  11. Wey tarik! Iyesusen lemegdlel siyabarerout ledjinetu neber...Ye eguiziabeher alama neberina, essu befelafotu heywetun sete, egnan lemadan sil. Setanem teshenefe selezih bechayen almotem belo teglun ketele...selezihim, Ethiopia be Egueziaber zend, temertalechena setanem yehen selemiyawek, liyatefa tenestoil...Iyessus en endassadedut, Tewahido Orhtodox en eyasadedu new...egnam, be tselotena be stome enetcherssachewalen...ye diabilos sera bizu new, letegereum sayhon, Geta wede ene nou eyale new...sele Nohe sil new, 1 nethsuh selenebere Eguiziaber liyaden yewessenew...Egnam netsuh kehonen, Geta yessemanal...Ateferu tseliyou be ewnetu Eguiziabeher Ke egna gar new, lezihim new, "Ethiopia edjochuan wede Eguiziabeher tezeregualetch " Yemilew, Geta yehe hulu fetena endemimetaben yawkal...ye he tenbit new, eyebassem lehed yetchelal lemen Geta yemefeligew ye Ethiopianwian ene lebe new...Wede ene temelessou, kefu sera tewu,alkessu temassenu Geta, Emebetachen be tselotoi, Tadenenalech...

    ReplyDelete
  12. I do agree with all of the concepts you've presented to your post. They're really convincing
    and will definitely work. Nonetheless, the posts are very short for starters.

    May you please extend them a bit from next time? Thanks for the post.
    my webpage :: social media monitoring definition

    ReplyDelete
  13. Have you ever considered about including a little bit more than just your articles?
    I mean, what you say is valuable and all. Nevertheless think about if you added some great pictures or video clips to give your posts more,
    "pop"! Your content is excellent but with images and clips,
    this website could undeniably be one of the best in its niche.
    Superb blog!

    Here is my page: info

    ReplyDelete
  14. memhir girma gar weseduat tedenalech

    ReplyDelete