Tuesday, July 3, 2012

የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠበቁ ማቴ. 7:15



 
አሸናፊ መኰንን (ዲ/ን)  - አንቀጸ ብርሃን  በሚል ስያሜ በሚያሳትመው መጽሔት ለአብነት ያህል ‹‹በእኛ ቤተ ክርስቲያን አምላክነቱን አጉልቶ የሰውነቱን ቅርበት መዘንጋት፣ በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የሥጋውን ቅርበት አግንኖ የመለኮቱን ክብር መርሳት የተለመደ ነው፡፡ መጽሐፉ ግን ያቻችለዋል፤›› "አባቶቻችን የመፍታትም ሆነ የማሰር ስልጣን የላቸውም " የሚሉና የመሰሉ በርካታ ክሕደቶችን ጽፏል አስተምሮአል፡፡ በመመሪያ ሓላፊ ደረጃ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና መዝገብ ቤት ሓላፊ ከኾነችውና ሙሉ ወንጌልቤተ እምነት ከምታዘወትረው / ዐጸደ ግርማይ ጋራ ጥብቅ ግንኙነት እንዳለው ይነገራል፡፡ በወ/ እጅጋየሁ በየነ አማካይነት በፓትርያሪኩ ልዩ /ቤት መሽጎ በበዓለ ሢመት፣ በዐበይት በዓላት፣ በደቀ መዛሙርት ምረቃ መርሐ ግብሮች ላይ በፓትርያሪኩ ስም የሚተላለፉ መልእክቶችን እስከ መጻፍ መድረሱ ይነገርለታል፡፡ በአሁን ሰዓትም ከበፊቱ በባሰ መልኩ የኑፋቄ ትምህርቱን በመዝራት ተያይዞታል ብዙ ምእመናንንም በማታለል በመውሰድ ላይ ይገኛል። አብረውትም ያሉ ብዙ መናፍቃንና እውነተኛ አባቶች ነን የሚሉ አብረውት ያሉ ሲሆን ምእመናንን ከሚያሳምኑበት አንዱም የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በመጥቀስ አብረውት የሚሰሩትን በመጠቆም እነርሱን ጠይቁ እንደሚልም ደርሰንበታል ስራውን ከኋላው ሆነው የሚረዱት በቤተ ክህነት ያለ አንዳንድ አባቶች እንዳሉ ተረድተናል።
 ይህ ሰው ከዚህ በፊትም ብዙ  ምእመናንን ስልጠና እየሰጠ እንደነበርና አሁን ለያዘው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ስራ ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ ብዙ ተሐድሶዎችን እንደመለመለ እየመለመለ እንደሆነ  ተረድተናል።
በበለጠ ሙሉ መረጃውን ከበቂ መረጃ ጋር ለወደፊት አናስነብባችኋለን ።
ቤተሰቦቻችሁንና ወንድም እህቶቻችሁን ከእንደዚህ ካሉት መናፍቃን እንዲጠበቁ መከሩ።
መረጃውን በማስተላለፍ የበኩሎን ይወጡ!!!

እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን ከመናፍቃን ይጠብቅልን።

9 comments:

  1. እግዚኣብሄር አፅራረ ቤተ ክርስቲያንን ያስታግስልን::

    ReplyDelete
  2. ቅዱስ ሲኖዶስ ያወገዛቸው 7(ሰባት) ግለሰቦች
    1. ጽጌ ስጦታው
    2. አሸናፊ መኰንን
    3. ደረጀ ገዙ
    4. በዛ ስፍርህ
    5. ግርማ በቀለ
    6. አግዛቸው ተፈራ
    7.‹መጋቤ ጥበብ› ሰሎሞን ጥበቡ
    ናቸው ምእመናኑ እንዲጠነቀቅ አሁን ያሉበት ሁኔታ በናውቀው ምእመናኑን ማስተማር መምከር እንችላለን እግዚአብሔር ይባርካችሁ ደቂቀ ናቡቴ

    ReplyDelete
  3. ሌባን ሌባ ነው ቢሉት ግብሩ ስለሆነ ትክክል ነው ተሐድሶንም ተሐድሶ ማለት ትክክል ነው ምክነያቱም ግብሩ ስለሆነ እግዚአብሔር ይስጥልን ። መረጃ ለሁላችንም ጠቃሚ ነው ስለዚህ በመረጃችሁ ቀጥሉበት ደቂቀ

    ReplyDelete
  4. መረጃው ጥሩ ነው ግን የተሳሳቱትን ለማረም የተናገሯቸውን ህፀፆች እንዲታረሙ ብታስተምሩን

    ReplyDelete
  5. በጣም ትክክል ነው!!! ግን ይሄ ተሃድሶ የሚለውን ተለጣፊ ስም እየሰጡም በከፊል የኦርቶዶከሳዊት ተዋህዶን ዶግማና ስርዓት በከፊል ይቀበላሉ የሚያስመስል ስም ይመስለኛል፡ ሙሉ ለሙሉ የቅዱሳንን ክብር የእመቤታችንን አማላጅነት እስከካዱና መድኋኔዓለምን አማላጅ ለማኝ ካሉ ታዲያ ጥርግ ብለው ከቤታችን ወጥተዋል ቢባል አይሻልም? እነሱ ከሌላ ቤት መጥተው ነው ቤታችሁን እናድስላችሁ የሚሉን እኮ! ለወደፊት በዙመረጃ እንደሚደርሰን እጠብቃለሁ! አመሰግናለሁ1

    ReplyDelete
  6. megemeriya endante yale xhewa asenafin leteche aychelem maferiya.

    ReplyDelete
  7. hello enante hesant ensdet nache ashun lekek argut berasachu tenbozabozu 100 gize endegena betefeteru esun atakelum

    ReplyDelete
  8. would you please post some evidences to the people of ethiopian orthodox tewahedo believers what the tehadesos are doing in our betekirstiyan if possible ye asenafin gude betawetubete tiru neber beteleye video weyem audio

    ReplyDelete
  9. I drop a comment each time I especially enjoy a
    article on a site or if I have something to
    valuable to contribute to the discussion. It's a
    result of the fire communicated in the article
    I read. And on this article "የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠበቁ ማቴ. 7:15".
    I was moved enough to write a commenta response ;) I actually
    do have 2 questions for you if it's okay. Could it be only me or does it appear like a few of the remarks
    look as if they are coming from brain dead visitors?
    :-P And, if you are writing at other places, I'd like to follow everything fresh you have to post.
    Would you list every one of your social pages like your Facebook
    page, twitter feed, or linkedin profile?


    Feel free to visit my homepage :: Louis Vuitton Online

    ReplyDelete