Friday, September 2, 2011

የተሐድሶ ሠራዊትነት ስልጠና ተሰጠ

‹‹ለቤተክርስትያን አገልጋዮች›› የተሐድሶ ሠራዊትነት ስልጠና ተሰጠ


በምስራቅ ኢትዮጵያ ከሚገኙ አራት ሀገረ ስብከቶች ለተውጣጡ ‹‹ለቤተክርስትያን አገልጋዮች›› የተሐድሶ ሠራዊትነት ስልጠና ተሰጠ



በማቴዎስ አጥምዛ (gebrher33@gmail.com)
  • የሥልጠናው ዋና ርዕሰ ጉዳይ ኢየሱስን ማለመመድ የሚል ነበር
  • ስልተ በጋሻው በዝርዝር ቀርቦላቸው እንዲጠቀሙበት መመሪያ ተሰጥቷቸዋል
  • ፓስተር መስፍን ፤ገበየሁ ይስማውና  በጋሻው ደሳለኝ ከነሐሴ 13-15 ሐረር በቆየበት ጊዜ በሥልጠናው ዙርያ መምከራቸውን ለመረዳት ተችሏል
  • ለሥልጠናው ተሳታፊዎች ኢየሱስ አማላጅ ነው የሚል ማስታዎሻ እና መጸሐፍ ተሰቷቸዋል
  • ከሠልጣኞቹ መካከል ቀደም ሲል ማኅበረ ቅዱሳን በክረምት ተተኪ መምህራን ሥልጠና አሰልጠኗቸው ከነበሩት ሠልጣኞች አንድ ግለሰብ ተገኝቷል
ከድሬዳዋ ፤ ከሱማሌ ፤ ከምዕራብ እና ምስራቅ ሐረርጌ አህጉረ ስብከቶች የኦርቶዶክስ  አብያተ ክርስቲያናት ለተውጣጡ ‹‹የቤተክርስቲያን አገልጋዮች›› ግበረ ተሐድሶን በሚያስፋፉበት ስልት ዙርያ ሥልጠና መሰጠቱን  በሰነድ እና በድምጽ ወምስል የደረሰው መረጃ አመለከተ፡፡
‹‹ሃይማኖቶችን አንድ እናደርግ ሁላችንም በቀን አንዳንድ ሰው እንለውጥ›› በሚል መርህ የተጀመረው ሥልጠና በሐረር ከተማ ሉትራን 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከነሐሴ 23-30 ሊሰጥ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ትላንት ማምሻውን መጠናቀቁ ታውቋል፡፡ሥልጠናው ዘወትር ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ምሽት 2፡30 እንደተሰጠ ለመረዳት ተችሏል፡፡የሰሌዳ ቁጥሩ ዕድ 00122 የሆነ ተሸከርካሪ ለሥልጠናው አስፈላጊ የሆኑ ሎጀስቲክስ ለማሟላት ሥራ ላይ ውሏል፡፡
የሥልጠናው ዋና አሰልጣኝ የቀድሞ የሐረር ቀበሌ 10 ሊቀ መንበር የአሁኑ ፓስተር መስፍን ነው፡፡ሌሎች ከአዲስ አበባ የተለያዩ የፕሮቴስታንት ድርጅቶች የመጡ በርካታ ፓስተሮች በአሰልጣኝነት የተሳተፉ ሲሆን ዋና አስታባባሪው ደግሞ ከአሰበ ተፈሪ ለዚሁ ሥራ ወደ ሐረር ያቀናው ገበየሁ ይስማው ነው፡፡ገበየሁ ይስማው በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ምንም የሥራ ኃላፊነት የሌለው ባለበት የሃይማኖት ችግር በተነሳ ውዝግብ በመቐሌው አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ የተማረውን የዲግሪ መርሀ ግብር ማስረጃ ያለተሰጠው ወልደ ተሐድሶ ነው፡፡በዚሁ ምክንያት በምዕራብ ሐረርጌ የይብሮ ወረዳ ኮተራ ቅዱስ ገብረኤል ምዕመናን አታስተምረንም በማለት እነዳባረሩት ይታወቃል፡፡ፓስተር መስፍን እና ገበየሁ ይስማው በጋሻው ደሳለኝ ከነሐሴ 13-15 ሐረር በቆየበት ጊዜ በሥልጠናው ዙርያ መምከራቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡
በሥልጠናው ዋና ትኩረት የተሰጠው ርዕሰ ጉዳይ ‹‹ኢየሱስን የማለማመድ ትምህርት›› ነው፡፡በዚህም ሠልጣኞቹ የበጋሻውን አሰረ ፍኖት እንዲከተሉ ተደጋግሞ ሲመከሩ ተስተውሏል፡፡ስልተ በጋሻው በዝርዝር ቀርቦላቸው እንዲጠቀሙበት መመሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
በሥልጠናው የተሳተፉት ግለሰቦች ከሐረር ከጅጅራ ከሰበ ተፈሪ እና ከድሬ ዳዋ ከተሞች የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ ሲሆኑ ከነዚህ መካካል ማኅበረ ቅዱሳን በ2000 ዓ.ም ክረምት በጅማ ለግቢ ጉባዔያት ተተኪ መምህራን አዘጋጅቶት በነበረው ሥልጠና ተሳታፊ የነበረ አንድ ግለሰብ ይገኝበታል፡፡ በቅርቡ አባ ሠረቀ ብርሃን በመቐሌ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ አካሂደውት በነበረው ውይይት አንድ የኮሌጁ ደቀመዝሙር ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ካህናት ማሰልጠኛ ምንፍቅና አስተምሮኛል›› ብሎ መናገሩን ያስታወሱ ታዛቢዎች ማኅበሩ የሠልጣኞች ምልመላ ስርዓቱን መሰፈተሽ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡
የሥልጠናውን ሙሉ ሂደት የሠልጣኞችን ዝርዝር የያዘ የሰነድ የፎግራፍ እና ቪዲዮ መረጃ ደርሶናል፡፡የተሐድሶን ሴራ በማጋለጥ የሚታወቀው ማኅበረ ቅዱሳንም መረጃው ተጠቃልሎ ደርሶታል፡፡የስልጠናው ተሳታፊዎች በቤተክርስቲያን አገልግሎት ከያዙት ቦታ እና ሊያደርሱት ከሚችሉት አደጋ አንጻር ማኅበሩ መረጃ አለኝ በሚል አጉል ብሒል እርምጃ ለሚወስዱ የቤተክርስቲያኒቱ አካል ፈጥኖ የማያደርስ ከሆነ ታሪክ የማይረሳው ስህተት እየፈጸመ እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚጠቀምበት ከሆነ ይህንን መረጃ ያጠናቀሩ የቤተክረስትያን ልጆች እንደ ሀዋሳ ምዕመናን የድርሻቸውን ለመወጣት ቪሲዲዎችን በማዘጋጀት ላይ ናቸው፡፡እንደ አግባብነቱ መረጃዎችን ወደ ፊት የምንገልጥ መሆኑን እያስታወቅን ይህንን መረጃ በመሰብሰብ እና ለተገቢው አካል በማድረስ ለተጉት የቤተክርስቲያን ልጆች ያለንን አድናቆት ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
‹‹እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን!!!! ››  by http://andadirgen.blogspot.com/2011/09/blog-post_9564.html

11 comments:

  1. እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን!!!!

    ReplyDelete
  2. AMLAKACHEN EGZIHABEHER BETECHRISTIANACHEN ENA ORTHODOXAWIYANEN YEBARKELEN YETEBEKELEN AMEN

    ReplyDelete
  3. የተሀድሶ ስልጠና ማለት የመናፍቅ ስልጠና ማለት ነው! ተሀድሶ ተብዬ እውር የሰይጣን አገልጋይ መናፍቅ በየ ቦታው ባታገሳ ምን አለበት? እንደናንተ አይነት ቂል ማን አለ? ሠይጣን አወቅሁህ ሲሉት ቢረዳ ምን አለ !!

    ReplyDelete
  4. እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን!!!!

    ReplyDelete
  5. እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን!!!!

    ReplyDelete
  6. Hello There. I found your blog using msn. This is an extremely well
    written article. I will be sure to bookmark it and return to
    read more of your useful information. Thanks for the post.
    I will certainly comeback.

    Feel free to surf to my web-site :: dolnoslaska agencja reklamowa

    ReplyDelete
  7. Becаuse mаssage іmρrоveѕ
    cirсulаtiοn аnd draws
    vital nutrіents to the skіn then it will dissolνе cemеnt and
    grout. After exploгing and taking photo's of the bubbling stops. Claudio Descalzi Okay The issue of police officers paying for sex is not a model for a successful tantra. We evolved from single cellular organism in to multi cellular organism and evolved as a form of courtesy to other clients and to protect people where to get a ride with someone else next time. Before we get ahead of ourselves, of our emotions.

    Here is my blog; head massage

    ReplyDelete
  8. Good day! This post could not be written any better!
    Reading this post reminds me of my good old room mate!
    He always kept chatting about this. I will forward this page to him.

    Fairly certain he will have a good read. Thank you for sharing!


    My weblog: reklamy lubin

    ReplyDelete
  9. Yes! Finally something about click.

    Feel free to visit my blog - barbour utility jacket sale

    ReplyDelete
  10. ›ÃÑ`UU Ñ>²?¨< eKÅ[c ’¨< ›eŸSÚ[h¨< ¾ì“ ÃÉ“M::
    ›Ó²=›wN?@` ÃÖwk”

    ReplyDelete
  11. You have astonishing info at this point.

    super fast reply - sneak a peek at these guys - on front page - just click the next site - use this link -
    Source - explanation - please click the next website - read
    this post here - Visit Webpage - discover here - source website
    - link - you could try these out - please click the up coming website
    page - related web site - why not try this out - just click
    the following internet page - just click the up coming document - Learn More Here
    - my review here - sneak a peek at this website - web link - visit the next document - look at here -
    look at this website - Click Link - look at this
    now - visit the following internet site - mouse click the up coming webpage - read review - recommended
    - just click the following article - Read More On this page - click the following web page - a cool way to improve
    - on the main page - read this - related resource site - click
    hyperlink - Full Write-up - their website - click now - mouse click on www.al3abflash.com -
    linked web site - Full Survey - click through the next
    site - go!! - have a peek at this web-site - click through
    the following post -

    http://www.firmakaydet.org/author/lonbeale684/ - http://www.havx888.top/comment/html/index.php?page=1u=226282 - http://khanthongboard.noads.biz/index.php?p=/discussion/465/institut-de-massage-lyon/p1 - http://yourbooki.com/?option=com_k2&view=itemlist&task=user&id=2248

    ReplyDelete